በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ማህበረሰብ እንዲፈጠር ከፍተኛውን ሚና የሚጫወተው ነፃ ፣ ገለልተኛ እና የታመነ የመረጃ ፍሰት ያለው የመገናኛ ብዙሃን መፍጠር የኢትዮጵያ አርታኢያንን በአንድ መድረክ እንዲሰባሰቡ ያስቻላቸው ራዕይ ነው፡፡ ይህ ታላቅ ራዕይ የወለደው ኢአማ በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ ላይ ወሳኙን ኃላፊነት የተሸከሙት አርታኢያን መሰባሰቢያ ጥላ በመሆኑ ከፍተኛ ኩራት ይሰማዋል፡፡

እርስዎም በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ መረጃን ለህዝብ በሚያደርሱ የህትመት ፣ የበይነ-መረብ እና የስርጭት ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ/የሰሩ አርታኢ ከሆኑ ፣ የዚህ ታላቅ አላማ ተጋሪ እንዲሆኑ በክብር እንጋብዝዎታለን፡፡ የኢአማ አባል መሆን ከፈለጉ ፣ እራስዎን ከዚህ በታች ከተጠቀሱት ሁለት መስፈርቶች ውስጥ ይፈልጉ፡፡

  1. መደበኛ አባል

በመደበኛ አባል መስፈርት ውስጥ የሚካተቱት አባላት ማንኛውም የአርታኢ ሙያ ደረጃ (ዋና አርታኢ ፣ አርታኢ ፣ ረዳት አርታኢ ፣ ዋና አዘጋጅ ፣ ረዳት አዘጋጅ…) ያላቸው ይሆናሉ፡፡ ተመሳሳይ የአርታኢያንን ስራ በጋዜጠኛ ማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ምሁራንም በመደበኛ አባልነት ሊቀላቀሉን ይችላሉ፡፡

  1. የክብር አባል

ከአምስት ዓመት በላይ በአርታኢነት ያገለገሉ ፣ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ከስራው የተለዩ የቀድሞ አርታኢያን የክብር አባል በመሆን ሊሳተፉ ይችላሉ፡፡ በዚህ መስፈርት ውስጥ ያሉት አባሎቻችን በማህበሩ የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ላይ ድምፅ የማይሰጡ እና የመምረጥም ሆነ የመመረጥ መብታቸው የተገደበ ይሆናል፡፡

ማንኛውም የአባልነት ማመልከቻ ተቀባይነት የሚያገኘው በማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ወቅት ሲሆን ፣ በአባልነት የሚቀላቀሉን አርታኢያን በኢአማ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት የአባልነት መዋጮ ይከፍላሉ፡፡

እርስዎም የኢአማ አባል መሆን ከፈለጉ ይህን ቅፅ ሞልተው እንዲያጋሩን በደስታ እንጠይቆታለን!